ከወረቀት ንክኪ ነጻ የሆነ አገልግሎት መስጠት የሚያስችል ቴክኖሎጂ ተመረቀ


ከወረቀት ንክኪ ነጻ የሆነ አገልግሎት መስጠት የሚያስችል ቴክኖሎጂ ተመረቀ


የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንዳሉት ÷ ቴክኖሎጂው የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ቀልጣፋና ተደራሽ ለማድረግ ከፍተኛ ሚና ይጫወታል፡፡

አሁን ላይም ቴክኖሎጂው በሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት፣ በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር እና በፕላንና ልማት ሚኒስቴር እየተተገበረ ይገኛል ብለዋል፡፡

በቀጣይ ወደ ሌሎች ተቋማት እና ክልሎች የማስፋፋቱ ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ነው ሚኒስትሩ ያስገነዘቡት፡፡

የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ኮሚሽነር መኩሪያ ኃይሌ (ዶ/ር) በበኩላቸው ÷ ቴክኖሎጂው ኮሚሽኑ እያከናወናቸው ለሚገኙ የሪፎርም ሥራዎች ትግበራ አጋዥ መሆኑን ተናግረዋል፡፡




Advertisement

Ad Space Available