የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በምርጫ ቦርድ ውሳኔ ላይ “ጊዜያዊ ዕገዳ” አሳለፈ
Author
amc-admin
Date Published

የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በምርጫ ቦርድ ውሳኔ ላይ “ጊዜያዊ ዕገዳ” አሳለፈ
የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በአማራ እና ትግራይ ክልሎች መካከል አከራካሪ በሆኑ አምስት የምርጫ ክልሎች ላይ ምርጫ እንዲያካሄድ ያሳለፈው ውሳኔ ላይ ጊዜያዊ ዕግድ ጣለ።
ምርጫ ቦርድ በሁለቱ ክልሎች መካከል አወዛጋቢ በሆኑ አምስት የምርጫ ክልሎች ከትግራይ እና ከአማራ ክልል ውጭ ሆነው በቀጥታ የተወካዮች ምክር ቤት ዕጩዎች ምርጫ እንዲካሄድባቸው ውሳኔ ያስተላለፈው ሰኞ የካቲት 16/2018 ዓ.ም. ነበር።
ይህንንም ተከትሎ በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው ዴሞክራሲያዊ ስምረት ትግራይ (ስምረት) ፓርቲ ባቀረበው አቤቱታ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሐሙስ የካቲት 19/2018 ዓ.ም. በውሳኔው ላይ ዕግድ ጥሏል።
በትግራይ የሚንቀሳቀሰው ስምረት ፓርቲ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ውሳኔን ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ይፋ ሲያደርግ በይፋ ተቃውሞውን በመግለጫ ያሳወቀ ሲሆን፣ ጉዳዩንም በፕሬዝዳንቱ አቶ ጌታቸው ረዳ በኩል ለፍርድ ቤት አቅርቧል።
የጠቅላይ ሚኒስትሩ የምሥራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ የሆኑት የቀድሞው የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ በማኅበራዊ ገጻቸው ላይ ባጋሩት በዚህ ውሳኔ ምርጫ ቦርድ መልሱን የካቲት 25/2018 ዓ.ም. እንዲያቀርብ ፍርድ ቤት አዝዟል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በአማራ እና ትግራይ ክልሎች መካካል አከራካሪ ሆነው የቆዩ የተባሉትን አምስት የምርጫ ክልሎች በተመለከተ ከፌዴሬሽን ምክር ቤት ደርሶኛል ያለውን ውሳኔ ይፋ ካደረገ በኋላ የሁለቱ ክልሎች ፖለቲከኞች ድጋፍ እና ተቃውሟቸውን ግልጸዋል።
#BBC

